Skip to content
Scan a barcode
Scan
Paperback የተራቡ የእግዚአብሔር ማዕደኞች (Amharic edition) [Afrikaans] Book

ISBN: B0GRG2PH1W

ISBN13: 9798250382434

የተራቡ የእግዚአብሔር ማዕደኞች (Amharic edition) [Afrikaans]

"የተራቡ የእግዚአብሔር ማዕደኞች" የተባለው ይህ መጽሐፍ እ.ኤ.አ በ2026 የተጻፈና የታተመ ነው። ይህን መጽሐፍ የጻፍኩበት ዋና ምክንያት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የደረሰብንን አደገኛ መንፈሳዊ ረሀብ ለማሳየት ነው። እንዲሁም ከሰማይ የሚመጣው የእግዚአብሔር ማዕድ ምን ማለት እንደሆነ፣ ማዕዱን የምንለይበት መንገድ፣ ማዕዱ በምድር ላይ የሚያከናውነው ተግባር ምን እንደሚመስል ከእግዚአብሔር የዘላለም አጀንዳ ጋር በማያያዝ በጥልቀት የተጻፈ ነው። በተጨማሪም አምስቱ የክርስቶስ ስጦታዎች በእግዚአብሔር ማዕድ ክርስቶስ በምድር ይሠራ በነበረበት የአላፊነት ክብደት ልክ ቀልድ የሌለውን ሥራ እንዲሠሩ የተጠሩ ናቸው። ታዲያ፦ ይህ ነው የማይባሉ በቊጥርም በዓይነትም ብዙ የተማሩ የነገረ መለኮት ምሁራን በየዘርፉ እያሉን ስለምን ተራብን? ስምን የተላበሱና የገነኑ ሐዋርያትና ነቢያት እያሉን እንዲት ልንራብ እንችላለን? ጥቅስን ከጥቅስ ጋር እያገናኙ የሚያስተምሩን ብዙ አስተማሪዎች በየስፍራው እያሉን ለምን በመንፈሳዊ ረሀብ ውስጥ ወደቅን? ለመንጎቻቸው የሰማዩን ምግብ እንዲመግቡ የተሾሙ እረኞች በየአጥቢያው እያሉን ለምን ጠኔ ያዘን? ለምን የእውነተኛው መንፈሳዊ ምግብ ጣዕም ጠፋብን? ሕዝቡን እናነቃቃለን በሚል አሳብ በብዙ ዋጋ አሉ የተባሉትን መዘምራንና የቃሉን አገልጋዮች በተደጋጋሚ ጋብዘን ለምን የሕዝቡ ረሀብ እየጨመረ መጣ? እኛም እንደ አይሁድ አለቆች በብዙ እውቀት የተሞሉ "የአብያተ ክርስቲያን ኅብረት" የሚባል ሸንጎ አለን፣ ጥያቄው፦ ይህ ሸንጎ ወይም ኅብረት እንደ ሐዋርያቱ ዘመን ሸንጎ ለሕዝቡ መንፈሳዊ ጥጋብን ያላመጣበት ምክንያት ምንድን ነው? የሚሉትን ጥያቄዎች የሚመልስ መጽሐፍ ነው።

Recommended

Format: Paperback

Condition: New

$17.00
Ships within 2-3 days
Save to List

Customer Reviews

0 rating
Copyright © 2026 Thriftbooks.com Terms of Use | Privacy Policy | Do Not Sell/Share My Personal Information | Cookie Policy | Cookie Preferences | Accessibility Statement
ThriftBooks ® and the ThriftBooks ® logo are registered trademarks of Thrift Books Global, LLC
GoDaddy Verified and Secured