ይህ አከራካሪ ጉዳይ መሆኑን እገነዘባለሁ። በዘመናችን የወንዶች እና የሴቶች ሚና ትልቅ ለውጥ ታይቷል። እኛ እኩል መሆናችን አይካድም ፣ ግን በቤተክርስቲያኗ አገልግሎት ውስጥ ሚናዎች ልዩነት አለ?
በዚህ ጥናት ውስጥ፣ እግዚአብሔር ለወንድና ለሴት በተፈጠሩበት ጊዜ ያለውን ዓላማ እና ያ ዓላማ በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን ውስጥ እንዴት እንደዳበረ በመመርመር እንጀምራለን። በተጨማሪም የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ልምምዶች እና በዚህ ርዕስ ላይ የሐዋርያው ጳውሎስ ትምህርቶችን እንመለከታለን።
ዛሬ የቅዱሳት መጻሕፍትን ትምህርት እና በቤተክርስቲያን ላይ ያለውን ተግባራዊነት በታማኝነት ለመገምገም ሞክሬአለሁ። በረከት እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።