በቃና ዘገሊላ መጽሐፍ ውስጥ ቅዱሳት መጻሕፍትን መሪ አድርገን በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት ውስጥ እንመላለሳለን፡፡ ከጌታችንና ከሐዋርያቱ ጋር ወደ ሰርግ ቤቱ እንገባለን፡፡ ወደ ጓዳ ዘልቀን የወይኑን ማለቅ አስበን እንጨነቃለን፣ እመቤታችን ስታማልድ ልጇም ሲማለድ እናያለን፣ ከአገልጋዮቹ ጋር ውኃ ልንቀዳ ወንዝ እንወርዳለን። አብረን ውኃውን እስከአፉ ሞልተን ጌታችን የሚያደርገውን እንጥብቃለን። ከታዳሚዎች ጋር ወይን የሆነውን ውኃ ቀምሰን እናደንቃለን። መልካሙን የወይን ጠጅ ምነው እስካሁን ቆየ? ብለን ከአሳዳሪው ጋር አብረን እንቆጫለን። ከዚያም ከሐዋርያቱ ጋር በስሙ አምነን ከሰርግ ቤቱ እንወጣለን። ከምድራዊው ሰርግ ቤት ወጥተንም ወደ የቤታችን ሳንገባ ወደ ሌላ ሰማያዊ ሰርግ በዚሁ መጽሐፍ ውስጥ እንታደማለን።
መልካም ንባብ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
Related Subjects
Bible Bibles Biblical Christian Christian Books & Bibles Christianity Religion Religion & Spirituality