እምነት ታሪካዊ ልብ ወለድ
በዶ/ር ዮሐንስ ተክሌ
"ሰውን መውደድ ባንቺ ጀምሬ ባንቺ እደመድመዋለሁ። ሰውን የሚያክል ግዙፍ ፍጡር ምን ያህል ግብዝ እንደኾነ፣ ብዙ ትምህርት ባንቺ አግኝቼአለሁ።
ያውም በመጀመሪያ የፍቅር ትውውቄ፣ ለመውደድና ለትዳር ያበቃኝ .." "የመጨረሻዋ የፍጡራን ርካሽ፣ ነውረኛ ነሽ። በተንኮንል የተገነባሽ ግፈኛ ነሽ። መሰሪ ደካማ ፍጥረት ነሽ። ለስሜትሽ ተገዢ.... እንደኔ ዐይነቱን ባል ከቶውንም በመብራት ፈልገሽ አታገኚም ..."
"...እኔ ሰግጄልሻለሁ እንደ ጣዖት አምልኬሻለሁ በፍቅር ታውሬ ... ብቻ ንጹሕ ፍቅሬን ያሰናከልሽው ሰይጣን ነሽ። ሰብአዊ ክብሬን የገፈፍሽ ዲያቢሎስ፣ ለቋሚ ፍቅር ያልታደልሽ".....እንደ ኦቴሎ ጨካኝማ ብኾን ኖሮ፣ ያንቺ ዕጣ የዴዝዴሞና ነበር። ያውም ሞት ግን አልኾንኩም። ስለምወድሽ ሳይኾን ያልጨከንኩብሽ፤ የጓደኛዬን የሰሎሞንን ቃል ስለማከብር ነው። የርሱ ቃል ለእኔ እንደ እግዚአብሔር ቃል ባይኾንም አከብረዋለሁ። ....